ሰው “ዕረፍት አግኝቻለሁ፤ አሁን ያለኝን እየበላሁ እኖራለሁ” ሲል ምን ያህል ጊዜ እንደሚቆይ አያውቅም፤ ገንዘቡን ለሌሎች ትቶ ይሞታል።
ያርፍ ዘንድ ተስፋ ባደረገ ጊዜ፥ “እበላለሁ እጠጣለሁ፥ እንግዲህስ ደስ ይለኛል፥ በቃኝም” ባለ ጊዜ፥ የሚሞትባትን ቀን አያውቅም፤ ገንዘቡንም ሁሉ ለባዕድ ትቶ እርሱ ይሞታል።